Event

የልቦና ውቅር(Mindset)


ለወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ መደበኛ ተማሪዎች በውቅረ ልቦና /ማይንድሴት/ ላይ ትኩረት ያደረገ የማነቃቂያ ስልጠና ተሰጥቷል።

ስልጠናው መቀመጫውን ደቡብ ኮርያ ካደረገው ዓለም አቀፍ የወጣቶች ህብረት /International Youth Fellowship/ከተሰኘ ግብረሰናይ ድርጅት በመተባበር የተዘጋጀ መሆኑ ተመላክቷል።

በመድረኩ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ታከለ ታደሰ እንደገለጹት፡ በልቦና ውቅር (ማይንድሴት) ላይ ግንዛቤን መስጠት ለጠንካራ አመለካከት እና ስብዕና ግንባታ ጉልህ ፋይዳ እንዳለው ተናግረዋል።

“ከፍ ያለ ዓላማ አንግበን ውጤት ለማስመዝገብ መስራት መቻል አለብን” ያሉት ፕሮፌሰር ታከለ፤ ትጉህ፣ ታታሪ እና ውጤታማ አገልጋይ እንድንሆን ስልጠናው አጋዥ በመሆኑ ትኩረት ሰጥተን እንከታተል በማለት መልዕክት አስተላልፈዋል።

በኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ ወጣቶች ህብረት (International Youth Fellowship) አስተባባሪ የሆኑት ዶክተር ናም ፒል ህዩን ለተማሪዎች ስልጠናውን የሰጡ ሲሆን፤ ውስን ሃብቶች ላይ ትኩረት በመስጠትና በመቀናጀት ደቡብ ኮሪያ ከነበረችበት ድህነት ተላቅቃ አሁን ወዳለችበት ብልፅግና እንዴት እንደደረሰች ገለጻ ሰጥተዋል፡፡

ተማሪዎች በትምህርት ቆይታቸው ሊኖራቸው ስለሚገባ ዲሲፒሊን፤ አሉታዊ እና ጠቃሚ ያልሆነ አስተሳሰብን በመለወጥ አዎንታዊ አመለካከትን ስለማዳበር እንዲሁም በሀገር ጉዳይ ገንቢ አስተዋጽኦን ከማበርከት አንጻር ኃላፊነታቸውን ለመወጣት መነሳሳት በሚፈጥሩ ርዕሰ ጉዳዮች ስልጠናው ተሰጥቷል።

ሀገርን ብሎም ዓለምን ለማልማት የሳይንሳዊ እውቀት፣ ቆራጥነት፣ ተነሳሽነት እና የዳበረ ቅንጅታዊ አሰራር አስፈላጊ መሆኑን ዶክተር ናም ፒል ህዩን ለተማሪዎች ተናግረው፤ በአጠቃላይ የማይንድሴት/የልቦና ውቅር ስልጠና ሁሉን አቃፊ፣ አገናኝ፣ አነቃቂ፣ ለፈጣን እና ዘላቂ ለውጥ መሰረት መሆኑንም ጠቁመዋል።

“ጥልቅ የማሰብ ችሎታን መጨመር፣ ጠንካራ አስተሳሰብን ማዳበር እና በመለዋወጥ የአንድነት ኃይልን መገንባት” ለውቅረ ልቦና/ማይንድሴት መሰረት መሆኑ በስልጠናው ተብራርቷል።

የስልጠናው ተሳታፊ ተማሪዎች በውቅረ ልቦና/ማይንድሴት ላይ ትኩረት ባደረገው የማነቃቂያ ስልጠና የተካተቱ ርዕሰ ጉዳዮች ጉልህ አዎንታዊ አስተሳሰብን ለማዳበር የሚረዱ፣ በቀጣይ የሕይወት ጉዞ ስርነቀል አዎንታዊ ለውጥ እንድናመጣ የሚያስችል እና ኃላፊነትን በአግባቡ ለመወጣት ግንዛቤን የሚፈጥር ነው ሲሉ ተናግረዋል።

#ኡማ_ኘሮሞሽን_እና_ኢቨንትስ ይህን መደረክ እንደ ተጠበቀው በብቃት በመምራት ለመድረኩ ስኬት የራሱን ድርሻ ተውቷል፡፡

#ኡማ_ኘሮሞሽን_እና_ኢቨንትስ

⬧︎ለደማቅ የመድረክ መምራትና ማማከር ሥራ

⬧︎ለሬድዮ እና ቴሌቪዝዥን ማስታወቂያዎች

⬧︎ለዶክመንታሪ ፊልም ዝግጅት

⬧︎ለሮድሾውሥራ

አጠቃላይ የሚዲያ ማማከር አገልግሎት

ፍላጎት ሲኖርዎ በ0911764351/0920464748 ይደውሉ አልያም

ወላይታ ሶዶ 21 ማዞሪያ ጥላሁን ሞል ቢሮ ቁጥር 218 በአካል ብቅ ይበሉ::

የልቦና ውቅር(Mindset) Read More »

ኡማ ፕሮሞሽን እና ኢቨንትስ የአብስራን ሆቴል ምርቃት በብቃት በመምራት አጠናቋል።

በልማታዊ ባለሀብት አቶ አዳነ ሹመቴ የተገነባው የአብስራ ሆቴል በደማቅ ፕሮግራም ተመረቀ።

በዎላይታ ሶዶ ከተማ የሆስፒታል ፣ ባንክ እና ሆቴል አገልግሎት የሚሰጠው ህንጻው የከተማውን የንግድ ስራ እንደሚያቀላጥፍ ተገልጿል።

ኡማ ፕሮሞሽን እና ኢቨንትስ ይህንን ደማቅ የምረቃ ስነስርዓት ከመድረክ ዝግጅት እስከ ፕሮግራም መምራት ድረስ በባለሞያዎች ታግዞ አሰናድቶታል።

“ባለሀብቱ አቶ አዳነ ሹመቴ ከአንድ መቶ ሚሊየን ብር በላይ ወጪ በማድረግ የገነቡት ህንፃ ለዎላይታ ሶዶ ከተማ ተጨማሪ የልማት አቅም መፍጠሩን የዞኑ አስተዳዳሪ አቶ አክሊሉ ለማ አስታውቀዋል።

አቶ አክሊሉ አክለውም በዛሬው እለት የተመረቀው ህንፃ የልማት መነሳሳትን የፈጠረ ነው ሲሉም ተናግረዋል ።

ከወቅታዊ የልማት ሁኔታ ልዩ ትርጉም የሚሰጠው ስለመሆኑ ያብራሩት አቶ አክሊሉ የጤና ቱሪዝም እንቅስቃሴ አንፃርም ተጠቃሹ ግሬስ ሆስፒታል ለዎላይታ እና አጎራባች ህዝባች በዚሁ ህንፃ ላይ አዲስ ትሩፋት ይዞ መጥቷል ብለዋል።

የትኛውም ኢትዮጵያዊ ዘር እና ብሄር ሳይለይ በአቃፊነት እና አብሮነት ለለውጥ በመስራት የሚታወቀው የዎላይታ ህዝብ የልማት ብስራት ሆኖ እንደሚቀጥል የዞኑ አስተዳደሪ አቶ አክሊሉ አስረድተዋል።

የዎላይታ ሶዶ ከተማ ከንቲባ አቶ ተመስገን አለማየሁ
አሁንም በከተማችን ተስፋ ሰጪ ኢንቨስትመንቶች አሉ ሲሉ ተናግረዋል።

በአምራች ኢንዱስትሪ እና በተለያዩ ዘርፎች የሚያለሙ ባለሀብቶችን ፈጥነው እንዲሰሩ እናበረታታለን ሲሉም ክቡር ከንቲባው ገልፀዋል።

አቶ ተመስገን ዛሬ የተመረቀው የአብስራ ሆቴል ምቹ የማረፊያ አማራጭ ከመሆኑም ባሻገር በፈጣን ግንባታ መጠናቀቁ ልዩ ያደርገዋል ብለዋል።

በርካታ የስራ እድል የፈጠረው የአብስራ ሆቴል
የከተማውን ኢኮኖሚ እና ገፅታ በጉልህ እንደቀየረው ከንቲባው አቶ ተመስገን ገልፀዋል።

አልሚው ባለሀብት አቶ አዳነ ሹመቴ ባስተላለፉት መልእክት ለህዝብ እና ለዎላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ምስጋና አቅርበዋል።

ዎላይታ የሁሉም ብሄሮች መኖሪያ እና ልዩ ሰላማዊ ስፍራ መሆኗን ከ1986 ጀምሮ ኖሬ አይቻለሁ ሲሉ ስራ ወዳዱ ባለፀጋ አቶ አዳነ ተናግረዋል።

አቶ አዳነ የከተማውን ገቢ እና ገፅታ ግንባታ እያሻሻለ ከሚገኘውን የአብስራ ሆቴል በተጨማሪ ሌሎችም ኢንቨስትመንቶችን ለማካሄድ እንደሚሰሩ ጠቁመዋል።

ለስራው ስኬታማነት የገንዘብ የእውቀት እና ሞራል ድጋፍ ያደረጉትን ሁሉም ባለድርሻዎች የአቶ አዳነ ባለቤት ወይዘሮ አለምነሽ አባይነህ አመስግነዋል።

በምረቃ ፕሮግራሙ ላይ አቶ አዳነ እና ቤተሰቦቻቸው
ለኢንቨስትመንት ያላቸውን ተነሳሽነት እና ፈጣን ልማትን የመተግበር አቅምን እውቅና እና ልዩ ልዩ ሽልማት ተሰጥቷቸዋል።

በእለቱ የተገኙ የስራ ባልደረቦቻቸው እና ህብረተሰቡ አቶ አዳነ  አስተዋይ አባት እና አቅመ ደካሞችን የሚደግፉ መሆናቸውን መናገራቸውን የዎላይታ ሶዶ ከተማ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች  ፅህፈት ቤት ዘግቧል።”

ኡማ ፕሮሞሽን እና ኢቨንትስ የአብስራን ሆቴል ምርቃት በብቃት በመምራት አጠናቋል። Read More »

Scroll to Top